የመጽሐፍ ቅዱስ ንባብ ፕሮጀክቱ ዓላማ

 

  • የዚህ ስራ ዋናው ዓላማ መጽሐፍ ቅዱስ ለሰዎች ሁሉ እንዲዳረስና የእግዚአብሔር ቃል መልእክት ከዚህ ቀደም እድል ላልነበራቸው ሰዎች ሁሉ እንዲዳረስ ማድረግ ነው!
  • ከዚህ ቀደም ያልተሰራው ስራ ላይ በማተኮር መላ መጽሐፍ ቅዱስን በድምጽ ለመደመጥ ማብቃት!
  • በተጨማሪ ሙሉው መጽሐፍ ቅዱስ በአውዲዮ በኤም.ፒ.ስሪ. ፎርማት በዲቪዲ መዘጋጀቱ እግዚአብሔርን ቃል ለማጥናት፣ ለማሰላሰልና ለማሰብ አመቺ መንገድ በመሆኑ ወገኖችን ሁሉ እንዲሁም ተከታዩን ትውልድ ይጠቀም ዘንድ ነው።

 

ስለመጽሐፍ ቅዱስ ንባብ በአውዲዮ ኤም.ፒ.ስሪ ጥቂት መረጃዎች፤

  • ከሁሉ አስቀድሞ ይሄንን የከበረ ስራ እንድንሰራ እኛን ታናናሾችን ልጆቹን ያደለንንና በእጃችን ይህ ስራ እንዲከናወን ያደረገውን አምላካችንን እግዚአብሔርን በክርስቶስ ኢየሱስ ስም እናመሰግናለን! ክብርና ምስጋና ሁሉ ለእርሱ ብቻ ይሁን! ያለእርሱ እርዳታ ይሄንን ቀርቶ ትንሿን ነገር እንኳን ማከናወን ባልተቻለን ነበረና!
  • ለመጀመሪያ ጊዜ የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ በሙሉ በአውዲዮ በኤም.ፒ.ስሪ. ፎርማት በአንድ ዲቪዲ ተዘጋጅቶ መውጣቱ ታላቅ ታሪካዊ ነገር ነው!
  • አዲስ ኪዳን ከዚህ ቀደም የነበረና ያለ ሲሆን ብሉይ ኪዳን በንባብ ሲዘጋጅ ይህ መጀመሪያ ጊዜው መሆኑን የኢትዮጵያ መጽሐፍ ቅዱስ ማሕበር ገልጾልናል።
  • የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ 1954ቱ (እ.ኤ.አ. 1962ቱ) እትም ልክ 47 ዓመት ሲሞላው ለመጀመሪያ ጊዜ መላ መጽሐፍ ቅዱስ በድምጽ ለመደመጥ በቅቷል!
  • የመላው መጽሐፍ ቅዱስ ይዘቱ 2.9 ጊጋባይት ያህል ነው!
  • የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጽሐፍት ንባቦቹ 20 በሚሆኑ የተለያዩ አንባቢያን ተነበው ተዘጋጅተዋል!
  • ከ30 በላይ ግለሰቦች በዚህ ፕሮጀክት ከ2003 ዓ.ም. ጀምሮ ተሳታፊ ሲሆኑ መላውን መጽሐፍ ቅዱስ አንብቦ፣ አርሞና አስውቦ በአውዲዮ ለማዘጋጀት የወሰደው በከፍተኛ ትኲረት ወደ ሶስት ዓመት ጊዜ ነው።
  • 66ቱን መጽሐፍት አዳምጦ ለመጨረስ የሚወስደው ጊዜ 88 ሰዓት ያህል ነው!
  • ይሄንን ንባብ ልዩ የሚያደርገው
    • የጽሑፉ ባለቤት በሆው በኢትዮጵያ መጽሐፍ ቅዱስ ማሕበር ፍጹም ፈቃድና ባርኮት የተዘጋጀ መሆኑ
    • በተቻለ መጠን ድራማዊ የንባብ ስልትን የተከተለ መሆኑ
    • በኤም. ፒ. ስሪ. ፎርማት መዘጋጀቱ (በስልክ፣ በኤም.ፒ.ስሪ. ማጫወቻ፣ በዲቪዲ ማጫወጫ፣ ወ.ዘ.ተ.) በማንኛውም ስፍራ ለማዳመጥ ተመቻችቶ የተውሰራ መሆኑ!
  • በዚህ አጋጣሚ የዚህ ቅጂ ገቢ ለቤተክርስቲያናችን የሕንጻ ስራ አስተዋጽኦ ለማድረግ ታስቦ የሚውል እንደመሆኑ ከዋጋው (150:-SEK) በላይም ቢሆን ለመክፈል ዝግጁ ነኝ የምትሉ ወገኖች ገቢው ለጌታ ስራ ስለሆነ በነጻነት አስተዋጽኦአችሁን ለማድረግ እንዳትከለከሉ በጌታ ፍቅር እናሳስባለን!
  • ወደፊትም ይህ ስራ ይቀጥላል! ከዚህ በኋላ ባሉት ዓመታት እንደገና ይህ የተሰራውን ስራ ልንጎበኝ፣ ልናሻሽል፣ ጥራቱን ከፍ ለማድረግና ጌታ በረዳን መጠን ደግሞ በፊልምም የተደገፈ አድርገን ለማውጣት እናስባለን።
  • አስተያየታችሁን፣ የእርማት ሃሳባችሁን፣ ወ.ዘ.ተ. ብትልኩልን በትልቅ ደስታ እንቀበላለን! አድራሻችን፤ it-ministry@j-e-c.org ነው!

  • ስለ መጽሐፍ ቅዱስ ዲቪዲው አጠቃቀምን ዘርዘር ያለ የቴክኒክ ገለጻ እዚህ ጋር ማግኘት ትችላላችሁ

የኢ.ወ.ቤ/ክ የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ ንባብ ፕሮጀክት

የዲቪዲው ዋጋ ከነመላኪያው ምን ያህል ነው?

 

የዋጋ ሰንጠረዥ

የተለያዩ አገሮች ምንዛሪ

የአንድ ዲቪዲ

 ዋጋ

የዲቪደው ብዛት

የመላኪያው ዋጋ አውሮፓ ውስጥ

የመላኪያው ዋጋ ከአውሮፓ ውጭ

 አውሮፓ ውስጥ ከነመላኪያው

ከአውሮፓ ውጭ ከነመላኪያው

በስዊድን ክሮነር SEK

 

150 (SEK)

1

2

ከ2 በላይ*

55 SEK

55 SEK

95 SEK

65 SEK

65 SEK

105 SEK

205 SEK

355 SEK

215 SEK

365 SEK

በኢትዮጽያ ብር፤

50 (Birr)

1-2

2-9*

-

100 BIRR

100 + X*

-

150 BIRR

100 + X*50

በዶላር፤$

18 (USD)

1

2

ከ 2በላይ*

7.02

7.02

12.13

8.30

8.30

13.14 

25.02

43.02

26.30

44.30

በዩሮ

 

14 (EUR)

1

2

ከ2 በላይ*

5.23

5.23

9.03

6.18

6.18

9.98

19.23

33.23

20.18

34.18

በፓውንድ፡£

 

 

12 (GBP)

1

2

ከ2 በላይ*

4.66

4.66

8.04

5.50

5.50

8.89

16.66

28.66

17.50

29.50

በካናዳ ዶላር C$

18(CAD)

1

2

ከ2 በላይ*

8.15

8.15

14.08

9.63

9.63

15.56

16.15

44.15

 

17.63

45.63

*እስከ ግማሽ ኪሎ (500 gram)

  • ከግማሽ ኪሎ በላይ ከሆነ እንደ ታዘዘው ቁጥር መጠን መላኪያው ስለሚጨምር በምታዙበት ጊዜ ዋጋውን እናስታውቃችኋለን

እንዴት ማዘዝ እችላለሁ?

  • ዲቪዲውን(ዎችን) ለማዘዝ የሚከተለውን  አድራሻ (ሊንክ) ስትጫኑ የምታገኙትን ቅጽ ሞልታችሁ ብትልኩልን ትእዛዛችሁን በተጻፈው የፖስታ አድራሻ እንልክላችኋለን። ይህ እምቢ ካላችሁ ግን የሚከተለውን አድራሻ ኮፒ አድርጋችሁ ኢንተርኔት ለመግባት በምትጠቀሙበት ፕሮግራም (ዌብ ብራውዘር) የአድራሻ መስጫ ውስጥ የሚከተለውን አስገብታችሁ ኤንተርን ተጫኑ፤
  • በዚህ መልኩ ትእዛዛችሀን ለመመዝገብ በሆነ ችግር ምክንያት ባይሳካላችሁ በኢሜይል (jec@j-e-c.org) ልታገኙን ወይም በታች በተሰጠው ስልክ ወንድም ወሰን ተሾመን ልታነጋግሩ ትችላላችሁ።

    • ስልክ፡+46-8-208491 ወይም +46-736162913 ከማክሰኞ እስከ ዓርብ ከ9.00 አስከ 16.00 ሰዓት(9.00a.m- 4.00p.m ) ድረስ
    • ፋክስ +46-8-100243

እግዚአብሔር ይባርካችሁ!

የገንዘብ አከፋፈል፤

  • በሐዋላ ወይም በ(money order) በባንክ በኩል ብትልኩልን እዚህ አገር ያልተለመደ በመሆኑ ምክናያት ገንዘቡን ለማግኘት ስለምንቸገር በሚከተለው መንገድ እንድትልኩልን አደራ እንላለን

  • በምታዙት ዲቪዲ ቁጥር መጠን ሂሳቡን በማስላት ገንዘቡን ከላይ ከተዘረዘሩት የምንዛሬ አይነቶች (በስዊድን ክሮነር፣ በዶላር፣ በዩሮ፣ በፓውንድ ወይንም በኢትዮጵያ ብር) በአንዱ ክፍያችሁን አስልተን በኢሜል ልትከፍሉ የሚገባችሁን መጠን ስለምንልክላችሁ በኢሜል የተገለጸውን የገንዘብ ልክ በፖስታ ውስጥ በማሸግ በሚከተለው አድራሻ እንድትልኩልን እንጠይቃለን።

Jerusalem Evangelical Church IT-Ministry

C/O Wossen Teshome

Wallingatan 3B, 3tr

111 60 Stockholm

SWEDEN

  • ከ4 ዲቪዲ በላይ ለምታዙ በዌስተርን ዩኒየን (Western Union) በኩል ብትልኩልን እንመርጣለን::

  • ከዚህ በተረፈ ግን በቀጥታ በባንክ በኩል ገንዘብ ልታዘዋውሩና ክፍያዎቻችሁን ለትፈጽሙ ለምትወዱ ወገኖች የሚያስፈልጓችሁ መራቻዎች እነሆ፤

    • IBAN SE 9195000099603407819543 och BIC-KOD (swift address) NDEASESS