.
ዋናው ገጽ > እኛ ማን ነን?

እኛ ማን ነን?

አገር/ብሔር

የኢየሩሳሌም ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን በስቶክሆልም ስዊድን የምትገኝ ኢትዮጵያውያንም ኤርትራውያንም አባላቶቻችን ያቀፈች አጥቢያ ስትሆን ከ200 መቶ ያላነሱ አባላቶች ያሉአት እ ኤ አ ከ1980 ዎቹ መጀመሪያ ጀምሮ በስቶክሆልም ስትንቀሳቀስ የኖረች የክርስቶስ ቤተክርስቲያን ናት::

ስነመለኮታዊ አቋም

የእምነት አቋማችን ካሪዝማቲክ ፔንቴኮስታል ሲሆን መጽሐፍ ቅዱስ ፍጹም የእግዚአብሔር ቃል እንደሆነ እናምናለን:: ስለእምነት አቋማችን በበለጠ ለማወቅ የእምነት መግለጫችንንና መሰረተ እምነታችንን እንዲሁም መተዳደሪያ ደንባችንን መመልከት ትችላላችሁ::

አመራር

ቤትክርስቲያናችን በመጋቢዎችና ሽማግሌዎች አገልግሎት ትመራለች::

ሳምንታዊ ፕሮግራሞች

  • ሐሙስና እንደየአካባቢው በሌላ የሳምንት ቀን: የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት (17:30 - 19:30)
  • በየሳምንቱ ቅዳሜ: የምሽት ፀሎት ጊዜ (18:00 - 20:00)
  • ዘወትር እሁድ: ዋና የአምልኮ ጊዜ: 10:00 - 13:00

አመታዊ ኮንፍራንሶች

በዓመት ሶስት ጊዜ ኮንፍራንሶች ያሉን ሲሆን በገና በፋሲካና በክረምት (ሰመር) ጊዜ ለየት ያሉ ስብሰባዎችን (ኮንፍራንስ) አለን:: በተለይ በክረምት (በሰመር) ወቅት የሚኖረን ኮንፍራንስ በአጠቃላይ በኖርዲክ አገሮች (ዴንማርክ ኖርዌ ስዊድንና ፊንላንድ) ከሚገኙ አጥቢያዎች ጋር አብረን የምናደርገው ስብሰባ ነው:: በተጨማሪም ቤተክርስቲያናችን የአውሮፓ ሕብረት አባል እንደመሆኗ በአውሮፓ ውስጥ ከሚገኙ እህት ቤተክርስቲያኖች ጋር የቤተክርስቲያን መሪዎች የተለያየ ልውውጥና ሕብረት አላት::

ንዑሳን ድረገጾች


ቋንቋ ምረጥ

ተጨማሪ ድረ ገጾች

ማስታወቂያዎች

መደበኛ (የዘወትር) ፕሮግራሞቻችን፤


  1. መጋቢዎቻችንን በሚከተለው ቁጥር ደውላችሁ ማግኘት ትችላላችሁ፤ መጋቢ ንጉሱ ጉሌ (+46 (0)735115951) መጋቢ ወሰን ተሾመ (+46 (0)736162913)

  2. ሰኞ 10:00-14:00 የምክር አገልግሎት በወንድም ሙሴ ሃይሉ (በስልክ ቁ. 0707568264) በመደወል ልታገኙት ትችላላችሁ።
  3. ዘወትር ረቡዕ ከጥዋቱ አራት ሰዓት (10፡00) እስከ አስር ሰዓት (15፡00) የጾምና የጸሎት ጊዜ አለን
  4. ሀሙስ 18:00—20:00 የመጽሓፍ ቅዱሰ ጥናት በተለያዩ አካባቢዎች ይካሄዳል:: እንዲሁም ቤተ ክርስቲያኒቷ ውስጥ አንድ የጥናት ቡድን ይኖራል
  5. በየሳምንቱ ቅዳሜ ከ18፡00 ሰዓት እስከ 20፡00 ሰዓት የምሽት ፀሎት ጊዜ አለን።
  6. ዘወትር እሁድ ከአራት ሰዓት (10፡00) እስከ አምስት ሰዓት ተኩል (11፡30) የታዳጊ ወጣቶች የአምልኮ ጊዜ በስዊድንኛ
  7. ዘውትር እሁድ ከአምስት ሰዓት (10፡30) እስከ ስድስት ሰዓት (11፡30) ድረስ የጸሎት ጊዜና
  8. ከአራት እሁድ ከስድስት ሰዓት (11፡30) እስከ ስምንት ሰዓት (13፡30) ድረስ የአምልኮ ጊዜ ይኖረና

  • ከ3 እስከ 12 ዓመት እድሜ ያላቸው ልጆች የሰንበት ትምሕርት ይሰጣቸዋል
  • ከ13 እስከ 18 ዓመት እድሜ ያላቸው ታዳጊ ወጣቶችን በየእሁዱ እናስተምራለን::
  • ከአስራ ስምንት ዓመት በላይ የሆናቸውን ስዊድንኛ ተናጋሪ ወጣቶች በአስራ አምስ ቀን አንዴ በዙም ረቡዕ ምሽት ፕሮግራም አላቸው

ክፍል ለማስያዝ ቤተክርስቲያን መሪዎች ይደውሉ:

የኢ. ወ. ቤ/ክ ሶሻል ሚድያ