.
ዋናው ገጽ > የአገልግሎት ቡድኖች > የርህራሄና የእርዳታ አገልግሎት

የርህራሄና የእርዳታ አገልግሎት

“ነገር ግን የዚህ ዓለም ገንዘብ ያለው፥ ወንድሙም የሚያስፈልገው ሲያጣ አይቶ ያልራራለት ማንም ቢሆን፥ የእግዚአብሔር ፍቅር በእርሱ እንዴት ይኖራል?” 1 ዮሐንስ 3፥17

የአገልግሎቱ ዓላማ

አገልግሎቱ የተጀመረው ከላይ በ1 ዮሐንስ 3፥17 ያለውን ክፍል መነሻ በማድረግ ሲሆን፤ ዋና ተግባሩም ክርስትያን ወንድሞችንና እህቶችን በሚያስፈልጋቸው ቁሳዊ ፍላጎቶች መርዳት ነው። የአገልግሎት ክፍሉም በዚህ ተግባር ውስጥ በረከት እንዳለ ያምናል።

የምናከናውናቸው ተግባራት

በአሁኑ ሰዓት አገልግሎቱ *** ቋሚ አባላት አሉት። እነዚህም አባላት በተለያየ ችግር ዉስጥ ለሚገኙ ወንድሞችና እህቶች ከተለያዩ የቤተክርስቲያኒቷ አካላት ጋር በመተባበር የተለያዩ ቸርነቶችን በየጊዜው ያደርጋሉ። ከእነዚህም መካከል፦

  • ማረፊያ ቦታዎችን ማዘጋጀት
  • የቤት ቁሳቁሶችን ማቅረብ
  • የአልባሳት ስጦታን መስጠት
  • የሥራ ዕድሎችን ማፈላለግ
  • ወዘተ...

የመሳሰሉትን ያጠቃልላል።

በተለያየ ምክንያት ችግር ከደረሰቦት ወይንም እርዳታ ከፈለጉ፤ ከታች የተጠቀሱትን የአገልግሎቱን አባላት በማናቸውም ሰዓት በአካል ወይንም በስልክ እንዲሁም በኢሜል ሊያነጋግሩ ይችላሉ።

አገልግሎቱን ለማገዝ

በስጦታዎ አገልግሎቱን ማገዝ ይፈልጋሉን? ማናቸውንም አይነት ቁሳዊ ወይንም የገንዘብ እርዳታ የአገልግሎቱ ክፍሉ በደስታ ይቀበላል። ይህንን ለማድረግ ልቦት ከተነሳሳ ፤ የአገልግሎቱን አባላት በማንኛውም ሰዓት ማነጋገር ይችላሉ።

የአገልግሎቱ አባላት

Habteselassie Abebe

wubalemasfaw01_101x0-1.0x100.jpg?nc=1458

ሐብተስላሴ አበበ

ውብዓለም አስፋው

ስልክ ቁጥር: 000 00 000 00

ኢሜል: ###@###.###


ቋንቋ ምረጥ

ተጨማሪ ድረ ገጾች

ማስታወቂያዎች

መደበኛ (የዘወትር) ፕሮግራሞቻችን፤


  1. መጋቢዎቻችንን በሚከተለው ቁጥር ደውላችሁ ማግኘት ትችላላችሁ፤ መጋቢ ንጉሱ ጉሌ (+46 (0)735115951) መጋቢ ወሰን ተሾመ (+46 (0)736162913)

  2. ሰኞ 10:00-14:00 የምክር አገልግሎት በወንድም ሙሴ ሃይሉ (በስልክ ቁ. 0707568264) በመደወል ልታገኙት ትችላላችሁ።
  3. ዘወትር ረቡዕ ከጥዋቱ አራት ሰዓት (10፡00) እስከ አስር ሰዓት (15፡00) የጾምና የጸሎት ጊዜ አለን
  4. ሀሙስ 18:00—20:00 የመጽሓፍ ቅዱሰ ጥናት በተለያዩ አካባቢዎች ይካሄዳል:: እንዲሁም ቤተ ክርስቲያኒቷ ውስጥ አንድ የጥናት ቡድን ይኖራል
  5. በየሳምንቱ ቅዳሜ ከ18፡00 ሰዓት እስከ 20፡00 ሰዓት የምሽት ፀሎት ጊዜ አለን።
  6. ዘወትር እሁድ ከአራት ሰዓት (10፡00) እስከ አምስት ሰዓት ተኩል (11፡30) የታዳጊ ወጣቶች የአምልኮ ጊዜ በስዊድንኛ
  7. ዘውትር እሁድ ከአምስት ሰዓት (10፡30) እስከ ስድስት ሰዓት (11፡30) ድረስ የጸሎት ጊዜና
  8. ከአራት እሁድ ከስድስት ሰዓት (11፡30) እስከ ስምንት ሰዓት (13፡30) ድረስ የአምልኮ ጊዜ ይኖረና

  • ከ3 እስከ 12 ዓመት እድሜ ያላቸው ልጆች የሰንበት ትምሕርት ይሰጣቸዋል
  • ከ13 እስከ 18 ዓመት እድሜ ያላቸው ታዳጊ ወጣቶችን በየእሁዱ እናስተምራለን::
  • ከአስራ ስምንት ዓመት በላይ የሆናቸውን ስዊድንኛ ተናጋሪ ወጣቶች በአስራ አምስ ቀን አንዴ በዙም ረቡዕ ምሽት ፕሮግራም አላቸው

ክፍል ለማስያዝ ቤተክርስቲያን መሪዎች ይደውሉ:

የኢ. ወ. ቤ/ክ ሶሻል ሚድያ